አርሰናል አትሌቲክ ቢልባኦን አሸነፈ

አርሰናል አትሌቲክ ቢልባኦን አሸነፈ
mifta juneidi Sep 17, 2025

አዲስ አበባ፣ መስከረም 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርሰናል በሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታ አትሌቲክ ቢልባኦን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።


በሻምፒየንስ ሊግ የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታ አርሰናል አትሌቲክ ቢልባኦን በሜዳው እና በደጋፊዎቹ ፊት ነው 2 ለ 0 ያሸነፈው፡፡


በመጀመሪያው የጨዋታ አጋማሽ ከባድ ፉክክር የገጠማቸው መድፈኞቹ ከእረፍት መልስ ተቀይረው የገቡት ማርቲኔሊ እና ትሮሳርድ ባስቆጠሯቸው ግቦች አሸንፈዋል፡፡


በተመሳሳይ ምሽት 1፡ 45 ላይ በተካሄደ ጨዋታ ፒ ኤስ ቪ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት በዩኒየን ሴንት ግሎዥ ተሸንፏል።


የመጀመሪያ ሳምንት ጨዋታዎች ቀጥለው ሲካሄዱ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቤኔፊካ ከካራበርግ፣ ጁቬንቱስ ከዶርትሙንድ፣ ሪያል ማድሪድ ከማርሴ እና ቶተንሃም ከቪያሪያል ይጫወታሉ።


አስተያየት ለመስጠት እባክዎ ይግቡ።

እስካሁን ምንም አስተያየት የለም። አስተያየት ለመስጠት የመጀመሪያው ይሁኑ!